Search results for - addis ababa

  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ

    Governmental Organizations

    በአዋጅ ቁጥር 35/2ዐዐ4 መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ተጠሪነቱ ለከተማው ከንቲባ ሆኖ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡- • የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲና ደረጃ በማገናዘብ የከተማውን የጤና አገልግሎት ደረጃ ያወጣል፣ ተግባራዊነቱን ያረጋግጣል፣ በጤና ጉዳዮች ላይ የግንዛቤ ማስፋፊያ ትምህርት ለከተማው ነዋሪ አመቺ በሆነ ዘዴ ይሰጣል ወይም እንዲሰጥ ያደርጋል፤ • አጠቃላይ የሆነ የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥርና ቅኝት ያደርጋል፣ ይቆጣጠራል፣ ይከላከላል፣ መረጃዎችን ያሰባስባል፣ ወረርሽኝ ሲነሳ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ይከላከላል፤

    011 515 3939 www.aahb.gov.et
  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት

    P.O.Box 57101
    Governmental Organizations

    በአዲስ አበባ ከተማ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር ዙሪያ ለሚሰሩ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ያልሆኑና የግል ድርጅቶች፣ የሐይማኖትና የማህበረሰብ ተቋማት በዋናነትም በግለሰብና ቤተሰብ አቅም በመገንባት፣ በማስተባበር፣ ለፕሮግራሞች አፈጻጸም የሚረዳ ሀብት በማሰባሰብና በማሰራጨት አፈጻጸሙን በተጠናከረ ሁኔታ በመከታተልና በመገምገም ተጋላጭ ተኮር የሆነ ውጤታማና የተቀናጀ የኤችአይቪ/ኤድስ የመከላከልና የመቆጣጠር አገልግሎቶችን ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ማቅረብ ነው፡፡

    011 550 2706
  • ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ

    Governmental Organizations

    ራዕይ በከተማ አስተዳደሩ የሚኖሩ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች፤በፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል በዋጋ ተደራሽ የሆኑ የጋራ መኖርያ ቤቶች ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ፤ ተልዕኮ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየውን ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ፡- * የመንግሰትና የቀበሌ ቤቶችን አስተዳደር በማሻሻል ቤቶቹ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ፣ * የጋራ መኖሪያ ሳይቶች በነዋሪው ሁለንተናዊ ተሳትፎ ፅዱና ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ የጋራ ፀጥታቸውና ሰላማቸው የተጠበቀ ሰላማዊ መንደር እንዲሆኑ ማስቻል፣ * የቤት ማስተላለፍ ስርአቱ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚጠቀም እንዲሁም ፍትሐዊነትን የተላበሰ በሁሉም ህ/ሰብ ተአማኒነት ያለው ማድረግ፣ * ለተጠቃሚዎች ከተላለፉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የገቢ አሰባሰብ ስርአቱ ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ እንዲሆን በማድረግ ለቤት ኘሮግራሙ ስኬት ተገቢውን ድርሻ መወጣት፣ * በመልሶ ማልማት የሚነሱ የመንግስት ቤት ተከራዮችን ፊታሃዊ በሆነ መልኩ አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ

    011 812 2366
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር

    Governmental Organizations

    የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አዲስ አበባ ስትቆረቆር የተመሰረተች ብትሆንም ለመኖሪያ ምቹ ያልሆኑ ሰፈሮችና ቤቶች የበዙባት ሆና ቆታለች፡፡ ይህንን የተጎሳቆለ ገፅታዋን ለመቀየርና ለዜጎች ምቹና ፅዱ የመኖሪያ አካባቢ ለመፍጠር በከተማ መስተዳደርራችን በተደረገው የመልሶ ማልማት ሥራ እና ከህዝቡ የልማት ተባባሪነት ጋር ተደምሮ ዛሬ ቂርቆስ ማታ ተዘርተው ጠዋት እንደ እንጉዳይ የሚበቅሉ በሚመስሉ ሰማይ ጠቀስ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን በጠበቁ ህንፃዎች እየተሞላች፣ እንደአዲስ እየተገነባች ትገኛለች፡፡ የመዲናችን አዲስ አበባ እምብርት የሆነችውና ታላላቅ ዓለም አቀፍ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና የቢዝነስ ማዕከላት መገኛ ሆና መዲናችንን ለዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከልነት የላቀ ድርሻ የምታበረክተው ቂርቆስ የነዋሪዎቿን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና የአገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎችን በማከዎን የሕዝብ ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት በየጊዜው ከፍተኛ መሻሻልና ለውጦች እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ የሀገራችን ዋነኛ ጠላት የሆነውን ድህነትና ኋላቀርነትን በማሸነፍ ሀገራችን የመካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍና ድህነትና ኋላ ቀርነትን ታሪክ ለማድረግ መንግስትና ሕዝብ ተቀናጅተው በጋራ ርብርብ እያደጉ ይገኛሉ፡፡ የክፍለ ከተማችንም አስተዳደርም የተገኙትን ድሎች በመጠበቅ ልማትና እድገቱ እንዲቀጥል ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ ሥራአጥ ዜጎችን በማኅበር በማደራጀት ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ ወደሥራ እንዲገቡ በማድረግ በርካቶች የራሳቸውን ሀብት እንዲፈጥሩና ከአነስተኛና ጥቃቅን ወደ መካከለኛ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ተችሏል፡፡ በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን የተጀመሩ የልማት የመልካም አስተዳደር እና የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ አጠናክሮ በመቀጠል የህዝብ አገልጋይነቱን ይቀጥላል፡፡ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር

    011 553 6513
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ

    P.O.Box 3328
    Governmental Organizations

    በ2012 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ የሥራ ሥምሪት አገልግሎት የተስፋፋባት፣ የኢንዱስትሪ ሰላም የሰፈነባት እና የህብረተሰቡ ማህበራዊ ጥበቃ የተረጋገጠባት ከተማ ማድረግ፡፡

    011 155 0244 www.bolsa.gov.et
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ

    ራዕይ በ2020ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በማደስ አዋጭና ውጤታማ የመሬት ዝግጅት በማከናወን የተሸሻለ የስራና የመኖሪያ አካባቢ በመፍጠር የከተማዋን ልማት እንዲፋጠን በማደረግ አዲስ አበባን አዲስ ማድረግ፡፡ የኤጀንሲዉ ተግባርና ኃላፊነት 1.በከተማዋ ክልል ውስጥ ለተለያዩ የልማት ሥራዎች የሚውል መሬት ያዘጋጃል፡፡ 2.በህዝብ ተሣትፎ የሚለማው እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማዋ የተጎዱና የደቀቁ አካባቢዎችን በመልሶ ማልማት ሥራ ያለማል፤ያድሳል፡፡ 3. ከተማው ውስጥ በልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችና መልሶ ማልማት ተነሺ ለሆኑት ተገቢውን የካሳ ግምት ይተምናል፤ የካሣ ክፍያ ይፈፅማል፤ ምትክ ቦታ ያዘጋጃል፤ 4. በመልሶ ማልማትና ለመሬት ዝግጅት ተፈላጊዉን መሠረተ ልማት ያጠናል፤ ለሚመለከታቸዉ ያሳዉቃል፤ ከገንቢዎች በሚገኝ ግብአት የግንባታ ቅንጅት ዕቅድና በጀት ያዘጋጃል፤ ሲፈቀድም ያስገነባል፡፡ አዋጅ ቁጥር 455/1997 መሰረት የካሳና የምትክ እና የልማት ተነሺ መብትና ግዴታ በተደነገገዉ መሰረት ይፈፀማል፤ ደንብቁጥር 135/1999፤ የካሳ መመሪያ ቁጥር 19/2006 መሰረት ቅድመ ሁኔታዎች፤ መብቶች፤ ግዴታዎች፤ ክልከላዎች በግልፅ የተደነገገዉን አሳታፊነትን እና ህብረተሰብ ተኮርና ልማት ተነሺን ተጠቃሚ ያደረገ እንዲሁም ተጠቃሚነትን መተግበር የሚያስችል አሰራርን የተከተለ ነዉ፡፡ የመልሶ ማልማት ሊካሄድባቸው የሚችሉትን የከተማዋን መሃል አካባቢዎች በመለየትና የአካባቢ ልማት ፕላን (LDP) በመስራት፣ ተነሺዎችን በተደጋጋሚ በማወያየትና በማሳመን፣ ቀልጣፋ እና ፍትሃዊ የምትክ ቦታ/ቤት አሰጣጥ እና የካሳ አከፋፈል ሥርዓትን በማስፈን በልደታ፣ በሰንጋተራ፣ በአራትኪሎ ባሻወልዴ፣ በፓርላማና በሌሎችም አካባቢዎች በጥቅሉ ከ360.12 ሄ.ር በላይ በሆነ መሬት ላይ የተለያዩ የመልሶ ማልማት ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከ20ሺ በላይ የልማት ተነሺዎችን በማስነሳት1.01 ቢሊየን ብር ካሳ በመክፈል ለ1,600 ተነሽዎች የማቋቋሚያ ድጋፍ የተሰጠ ሲሆን በሌላ መልኩ በመጀመሪያ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከ2006-2009 በጅት አመት ለተለያዬ አገልግሎት የሚውል የተዘጋጁ መሬቶች 5924.693 ሄ/ር መሬት ማዘጋጀት ተችሏል::

    011 156 4189
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር

    Governmental Organizations

    ወቅታዊና አስተማማኝ የሆነ የከተማዋን የመሬት መረጃ በመሰብሰብና በማቀናጀት እንዲሁም ዘመናዊ የአድራሻና የመረጃ ሥርዓት በመዘርጋትና በመጠቀም ለተለያዩ ተጠቃሚዎችና ዜጎች በማድረስ የመልካም አስተዳደርና የልማት ሥራዎች እንዲሳኩ የበኩሉን ድርሻ መወጣት፡፡

    011 550 0570
  • የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት

    Governmental Organizations

    ዲስ አበባ ከተማን በ2012 ዓ.ም ፍትሃዊ አስተዳደር የሰፈነባት የላቀ የልማት ስራዎች ተሰርተው ህብረተሰቡ ተጠቃሚ የሚሆንበት፣ጠንካራ የሃገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ያላት በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ 5 ከተሞች ተርታ እንድትስለፍ ማድረግ፡፡በመንግስት አካላት አገልግሎትና በከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት የረካ ህብረተሰብ ተፈጥሮ ማየት፡፡

    011 111 7422
  • በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ

    Governmental Organizations

    1. ራዕይ በ2017 የአዲስ አበባ ከተማ ሰፊ የሥራ ዕድልና የተሻለ ገቢ የፈጠሩ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት ሰፊ መሰረት የጣሉ፣ ልማታዊ አስተሳሰብ ያዳበሩ ብቁና ተወዳዳሪ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከተስፋፋባቸው የአፍሪካ ከተሞች ቀዳሚ ሆና ማየት፡፡ 2. ተልዕኮ ከዘርፉ ልማት አስፈፃሚና ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በራሳቸው ጥረትና በመንግስት ድጋፍ የሥራ ዕድል ለፈጠሩ ነባር የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተቀናጀ ድጋፍ በመስጠት ለኢንዱስትሪ ልማቱ መፋጠን መሰረት የሚጥሉ ኢንተርፕራይዞችን በማስፋፋትና በማጠናከር ዘርፉ ለመዋቅራዊና ፖለቲካል ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን የድርሻውን እንዲወጣ ማስቻል ነው፡፡ 3. እሴቶች * ለለውጥ ዝግጁነት * ግልጽነት * የህዝብ አገልጋይነት * ፍትሃዊነት * ሥራ ፈጣሪነት * ኪራይ ሰብሳቢነትን በጽናት መታገል * ተጠያቂነት

    011 126 2235 www.aamicrosmall.gov.et