በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር
አዲስ አበባ በ2012 ዓ.ም መካከለኛ ገቢ ካላቸው ከተሞ ች ጋር ተወዳዳሪ የሆነች ለኑሮ ምቹና የመልካም አስተዳደር ተምሳሌት እንድትሆን ማድረግ::
አዲስ አበባ በ2012 ዓ.ም መካከለኛ ገቢ ካላቸው ከተሞ ች ጋር ተወዳዳሪ የሆነች ለኑሮ ምቹና የመልካም አስተዳደር ተምሳሌት እንድትሆን ማድረግ::
የአዲስ አበባ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ በ2012 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማን የስርዓተ-ፆታ እኩልነት የሰፈነባት፣ የህፃናት መብት የተከበረባት ከተማ የማድረግ እና ስብዕናው የተሟላ በአገር ግንባታ ሂደት ተሳታፊና ተጠቃሚ የሆነ ዜጋ የመፍጠርን ራእይ ሰንቆ በህብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ በመፍጠርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ሕዝባዊ መሰረት ያላቸው አደረጃጀቶችን በማጠናከር የንቅናቄና ተሳትፎ ፕሮግራሞችን በመዘርጋት ማህብረሰብ አቀፍ የህፃናት ድጋፍና እንክብካቤ አገልግሎት በመስጠትና የህፃናትን ደህንነት በማስከበር እንዲሁም ሁሉም ሴክተር መ/ቤቶች የስርዓተ ፆታና የህፃናትን ጉዳይ በእቅዶቻቸው ውስጥ አካተው እንዲሰሩ በማድረግ እንዲሁም አፈፃፀሙን በጋራ በመገምገም የከተማዋን ሴቶች በሁሉም መስክ እኩል ተሳታፊ፣ ተጠቃሚና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የህፃናት መብትና ደህንነት እንዲጠበቅ በህብረተሰቡ ዉስጥ ያለዉን ትክክል ያልሆነ አመለካከት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ዉጤታማ ስራዎችን በቢሮዉ ስር ያሉ ተቋማት ለህፃናት መቆያነት ምቹ እንዲሆኑ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ወላጆቻቸዉን ያጡና ለችግር የተጋለጡ ህፃናትን ለአደራ ቤተሰብ ማለትም የተፈጥሮ ወላጆቻቸውን በመተካት የሚያሳድጉ ፈቃደኛ ቤተሰቦችን /አሳዳጊዎችን እንዲያገኙ በማድረግ አሊያም በሃገር ውስጥ ጉዲፈቻ ተተኪና ቋሚ የሆነ የቤተሰብ ክብካቤ እንዲያገኙ በማመቻቸት ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፎችን በማጠናከር በርካታ ህፃናት በሀገራችው፣ በማህበረሰቡ መካከል እንዲያድጉ በማድረግ ከህብረተሰቡ ፍቅር አግኝተዉና፣ የማህበረሰቡን ባህሎች፣ ወጎችና የአኗኗር ዘይቤዎች አዉቀዉ እንዲሁም ሃገር ወዳድ የሆኑ የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጎች ሆነው እንዲያድጉ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም ከህብረተሰቡ ከግማሽ በላይ የሆኑ ሴቶች እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በሁሉም የልማት መስኮቻችን በማካተት የሀገራችንን እድገት እናፋጥን፤ ቀጣይነቱንም እናረጋግጥ፡፡
አዲስ አበባ ኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዴቨሎፕመንት ኤጀንሲ የመንግስት ተቋም ሲሆን አላማው ከተማዋን በቴክኖሎጂ የታገዘ የኑሮ ዘይቤ ማስቻል ነው:: ከዚህ በተጨማሪም የከተማዋ ህዝብ ከጊዜው የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያረግ ማገዝ ነው::